ዘመን ባንክ የኢትዮጲያ ኔዘርላንድስ ቢዝነስ ማህበር (ENLBA) አባል በመሆን አብሮ ለመስራት የሚያስችላለውን ስምምነት ነሐሴ 22 ቀን 2024 ዓ.ም. በባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ተፈራረመ፡፡

ስምምነቱ ዘመን ባንክ የኢትዮጵያ – ኔዘርላንድ ቢዝነስ ማህበር (ENLBA) ስር ካሉ ዘርፈ ብዙ ኢንዱስትሪዎች ጋር የሚኖረውን አጋርነትን ከማጠናከሩም በላይ ባንኩ ዘላቂ የባንክ እገዛ እና አጋርነትን ከሚፈልጉ መሰል ተቋማት ጋር አብሮ የመስራት እቅዱን ለማሳካት ያሰችለዋል፡፡ በአንፃሩ ደግሞ ማህበሩ እና አባላቱ የዘመን ባንክን ዘመናዊ እና ፈጠራ የታከለበት የፋይናንስ አገልግሎት ተጠቃሚ ይሆናሉ።

Share