ዘመን ባንክ የፈረንሳይ ብሔራዊ ቀን ክብረ በዓል ላይ በአጋርነት ተሳተፈ::

ዘመን ባንክ በኢትዮጵያ የፈረንሳይ ኤምባሲ ሐምሌ 7 ቀን 2018 ባዘጋጀው የሀገሪቱ ብሔራዊ ቀን (ባስቲል ዴይ) ክብረበዓል ላይ በአጋርነት ተሳተፈ፡፡

በዝግጅቱ ላይ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት፣ የዓለምአቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች፣ በኢትዮጵያ የሚኖሩ የፈረንሳይ ዜጎችና ጥሪ የተደረገላቸው ከ900 በላይ እንግዶች ተገኝተዋል።

ዝግጅቱ በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ህብረት የፈረንሳይ አምባሳደር በሆኑት በሚ/ር አሌክሲስ ላሜክ የመክፈቻ ንግግር በይፋ የተጀመረ ሲሆን ዘመን ባንክ የዝግጅቱ ስፖንሰር በመሆኑ እውቅና ተሰጥቶታል።

ዘመን ባንክ፤ ዘላቂና ትርጉም ያለው አጋርነት ለመገንባት ቁርጠኛ  የሆነ ተቋም በመሆኑ፣ ከኢትዮጵያ የፈረንሳይ ኤምባሲና ከፈረንሳይ ማኅበረሰብ ጋር በመተባበር ይህን ብሔራዊ በዓል በጋራ በማክበሩ ደስታ ይሰማዋል።

Share